እንኳን ለ፳፻፪ ዓመተ ምሕረት ዐቢይ ጾም በሰላም አደረሰዎ። ክቡር አባታችን አለቃ አያሌው ታምሩ ጾምን፥ በተለይም ዐቢይ ጾምን በተመለከተ «የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት» በተባለው መጽሐፋቸው ካሰፈሩት የተገኘውን ትምህርት ይህንን ታላቅ ጾም ምክንያት በማድረግ አቅርበናል።
እንዲሁም ክቡር አባታችን የ፲፱፻፺ ዓመተ ምሕረትን ዐቢይ ጾም ምክንያት በማድረግ ለኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን የካቲት ፲፬ ቀን ፲፱፻፺ ዓመተ ምሕረት በወጣው ማዕበል ጋዜጣ አማካይነት ያስተላለፉትን መልእክት . . .
የተወደዳችሁ ምእመናን! እንኳን ለበዓለ አስተርእዮ በሰላም አደረሳችሁ።
መሠረተ ቃል፤ ‹‹ኵለንታኪ ሠናይት አንተ ኀቤየ፤ አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ። ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ አምሊባኖስ።» «የእኔ ሆይ ሁለንተናሽ ያማረ ነው፤ በአንቺ ላይም ምንም ምን ነውር የለብሽም። ከሊባኖስ ነዪ፤ እቴ ሙሽራ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ።›› (መኃ. ፬፥ ፯።)
የተወደዳችሁ ምእመናን! እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ።
ጾመ ገሃድ (ጋድ)፦ የቃሉ ትርጕም «ገሃድ» ሲል መገለጥ፥ «ጋድ» ሲል ለውጥ ማለት ነው። ቅዱሳን ሐዋርያት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱና የጥምቀቱ በዓል በሳምንት ሁለት ቀን በምንጾምባቸው ጾም በተሠራባቸው በረቡዕና በዓርብ የዋለ እንደ ሆነ የጾሙ ሥርዓት ሳይጠበቅ፤ . . .