በዓለ ትንሣኤ።
(ሚያዝያ ፲፩ ቀን ፪ ሺ ፩ ዓ ም)
«ተንሥአ በከመ ይቤ።» «እነሣለሁ እንዳለ ተነሣ።» (ማቴ፤ ም ፳፰፥ ቍ ፰።)
ሰው እግዚአብሔር የሰጠውን ትእዛዝ በመተላለፉ ምክንያት በሕይወቱ ሞት ተፈረደበት። «አንተ መሬት ነህ፤ ወደ መሬት ትመለሳለህ፤» ተባለ።
ማንኛውም ወንጀለኛ በሠራው ጥፋት ሲፈረድበት ሁለት ዐይነት መቀጫ አለ። ከእነዚህም አንዱ ሕግን በመተላለፉ የሚከፍለው መቀጫ ሲሆን፤ ሁለተኛው ለተበዳዩ የሚከፍለው ካሣ ነው። አዳም ሕግን በመተላለፉ በሥጋው ወደ መቃብር፥ በነፍሱ ወደ ሲኦል መውረድ ተፈርዶበት በሞተ ሥጋ፥ በሞተ ነፍስ ተቀጣ። ካሣ ግን የሚከፍለው አልነበረውምና እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ካሠለት። ስለዚህም ከሕይወት ወደ ሞት እንደ ሄደ ከሞት ወደ ሕይወት መመለስ ያስፈልገው ነበር። ስለዚህ ሰው የሆነው አምላክ በሞቱ ሞትን አጠፋለት። በመቃብሩም ሙስና መቃብርን አስቀረለት። በትንሣኤውም ትንሣኤን መሠረተለት። ይህን የቤዛነት ሥራ ለመፈጸም ክርስቶስ የሄደበትን የመስቀል ጉዞ ስንመረምር ከመሥዋዕትነቱ ማለት ከስቅለቱ፥ ከሞቱ ተነሥተን ትንሣኤውን ዕርገቱን እናያለን። ለሰውም የሰጠውን አዲስ ሕይወት እንመለከታለን።
ተጨማሪ።
ሰሙነ ሕማማት።
(ሚያዝያ ፭ ቀን ፪ሺ ፩ ዓመተ ምሕረት።)
ለ፪ ሺ ፩ ዓመተ ምሕረት ሰሙነ ሕማማት እንኳን አደረሰዎ። ሰሙነ ሕማማትን በተመለከተ አባታችን አለቃ አያሌው ታምሩ ካስተላለፏቸው ስብከቶች መካከል አንዱን ከድምፅ ማኅደር ውስጥ ማግኘት ይችላሉ። ወይም ይህንን ስብከት ለማውረድ እዚህ ላይ ይጫኑ። ይህ ስብከት ሚያዝያ ፫ ቀን ፲፱፻፹፰ ዓመተ ምሕረት ለጸሎተ ኀሙስ የተላለፈ ነው። አምላካችን ጾሙን በሰላም አስፈጽሞ ብርሃነ ትንሣኤውን ለማየት ያብቃን። አሜን።
ዐቢይ ጾም።
(የካቲት ፲፫ ቀን ፪ሺ፩ ዓመተ ምሕረት።)
እንኳን
ለ፪ሺ፩ ዓመተ ምሕረት ዐቢይ ጾም በሰላም አደረሰዎ። ክቡር አባታችን አለቃ አያሌው ታምሩ ጾምን፥ በተለይም ዐቢይ
ጾምን በተመለከተ «የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት» በተባለው መጽሐፋቸው ካሰፈሩት የተገኘውን ትምህርት ይህንን
ታላቅ ጾም ምክንያት በማድረግ አቅርበናል። ተጨማሪ።
እንዲሁም ክቡር አባታችን የ፲፱፻፺ ዓመተ ምሕረትን ዐቢይ ጾም ምክንያት በማድረግ ለኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን
የካቲት ፲፬ ቀን ፲፱፻፺ ዓመተ ምሕረት በወጣው ማዕበል ጋዜጣ አማካይነት ያስተላለፉትን መልእክት ከዚህ ማንበብ ይቻላል።
እግዚአብሔርአምላካችንጾሙንበሰላምአስፈጽሞብርሃነትንሣኤውንለማየትያብቃን።አሜን።
በዓለ ጥምቀት።
(ጥር ፲ ቀን ፪ሺ፩ ዓመተ ምሕረት።)
ጌታችን
አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለ፪ሺ፩ ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደትና በዓለ ጥምቀት በሰላም
አደረሰዎ። በዓለ ልደትን በተመለከተ ክቡር አባታችን ከሰጧቸው መግለጫዎች አንዱን በዚህ ድረ ገጽ ላይ ለማቅረብ
ያቀድን የነበረ ቢሆንም በበዓሉ ሰሞን በነበረው የኢንተርኔት መሥመር መጣበብ ምክንያት ያቀድነውን ለማድረግ ባለ
መቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን። አሁን ግን በዓለ ጥምቀትን በማስመልከት ክቡር አባታችን ጥር ፲፪ ቀን ፲፱፻፺፮
ዓመተ ምሕረት በኢትዮጵ ጋዜጣ አማካይነት ለኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን ያስተላለፉትን መልእክት ያቀረብን ስለ ሆነ
በጥሞና እንዲያነቡት እንጋብዛለን። እግዚአብሔር አምላካችን በዓሉን የተባረከ ያድርግልን፤ ለአገራችንም ሰላምንና
ብልጽግናን ያድልልን፤ አሜን። ተጨማሪ።
ዕንቍጣጣሽ፥ ርእሰ ዐውደ ዓመት።
(መስከረም ፩ ቀን ፪ሺ፩ ዓ∙ ም∙) |